Sunday, June 23, 2019

የአማራ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር መገደላቸው ተረጋገጠ

(23 Jun, (DW Amharic))--የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አምባቸው መኮንን እና የርዕሰ መስተዳድሩ የአደረጃጀት ዘርፍ አማካሪ አቶ እዘዝ ዋሴ መገደላቸውን የአማራ ክልል ቴሌቪዥን ጣቢያ አረጋገጠ። የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሆነው የተሾሙት አቶ ምግባሩ ከበደ በጥይት ቆስለው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አምባቸው መኮንን እና የርዕሰ መስተዳድሩ የአደረጃጀት ዘርፍ አማካሪ አቶ እዘዝ ዋሴ መገደላቸውን የአማራ ክልል ቴሌቪዥን ጣቢያ አረጋገጠ።

የክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በሰበር ዜናው ይፋ እንዳደረገው ከወራት በፊት የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሆነው የተሾሙት አቶ ምግባሩ ከበደ በጥይት ቆስለው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።

ጣቢያው ከዚህ ውጭ በዝርዝር ያለው ነገር የለም። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ትላንት ከእኩለ ለሊት በኋላ በብሔራዊው ቴሌቪዥን ቀርበው በሰጡት መግለጫ የአማራ ክልል ባለስልጣናት የተገደሉት እና የቆሰሉት በስብሰባ ላይ እያሉ እንደነበር መናገራቸው አይዘነጋም።
DW Amharic

No comments:

Post a Comment