Wednesday, July 31, 2013

ኢትዮጵያ በወሳኙ ጨዋታ ወሳኝ ተጨዋቾችን አታሰልፍም

(July 31, 2013, (አዲስ አበባ))--ኢትዮጵያ ከመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር በኮንጎ ብራዛቪል ላለባት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ አይናለም ሀይሉን፣ አዲስ ህንጻንና ጀማል ጣሰውን እንደማታሰልፍ ፊፋ አሳወቀ፡፡

ተጨዋቾቹ የማይሰለፉት በማጣሪያ ጨዋታዎች ካርድ የተመለከቱ በመሆናቸው እንደሆነ ፊፋ  አስታዉቋል፡፡ በጨዋታው የማይስለፉ ተጨዋቾችን ለመተካት ለብሄራዊ ቡድኑ ከባድ ፈተና እንደሚሆን እየተነገረ ነው፡፡

መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ በሀገሯ ያለውን አለመረጋጋት ምክንያት በማድርግ ከኢትዮጵያ ጋር የምታደርገውን ጨዋታ በኮንጎ ብራዛቪል  እንዲሆን ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን /ፊፋ/ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ በዚህ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማሸነፍ ካልቻለ የተፈጠረውን ጥሩ አጋጣሚ  የሚያጣ ይሆናል፡፡

ደቡብ አፍሪካና ቦትስዋና በሚያደርጉት ጨዋታ አቻ ከተለያዩ በቀጥታ ኢትዮጵያ ማለፍ የምትችል ሲሆን ከሁለት አንዱ አሸንፈው ኢትዮጵያ ከተሸነፈች ወይንም አቻ ከወጣች ከውድድሩ የምትሰናበት ይሆናል፡፡
ምንጭ፡ ኢሬቴድ

No comments:

Post a Comment