Sunday, June 09, 2013

የአዲስ አበባ የባቡር ፕሮጀክት ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል እየፈጠረ ነው

(June 09, 2013, (አዲስ አበባ))--በሃገሪቷ በዓይነቱ ለየት  ያለው የአዲስ በባው የባቡር ፕሮጀክት ለበርካታ ዜጎቸ የስራ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን ሲሲቴቪ ዘገበ፡፡

(ኢሬቴድ)
ይህ ፕሮጀክት  በአዲስ አበባ  የሚታየውን  የትራንስፖርት  ችግር  በእጅጉ ይቅርፈዋል እንደ ሲሲቴቪ ዘገባ፡፡ የኢትዮÉያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው በትሩ በረካታ ህዝብ  ባለበት ከተማ ውስጥ የወል ትራንስፖርትን  መጠቀም አማራጭ የሌለው መፍትሄ ነው  ብለዋል፡፡ አሁን  በአዲስ አበባ  በመገንባት ላይ ያለው የባቡር ፕሮጀክት በአንድ አቅጣጫ ብቻ 15ሺህ ተሳፋሪዎችን በሰዓት ማሰተናገድ ያስችላል ብለዋል፡፡

የዚህ ፕሮጅክት ስራ በሁለት ምዕራፍ  የሚጠናቀቅ ሲሆነ የመጀመሪያው ምዕራፍ  44 ኪሎሜተርት የሚሸፍን ሲሆን ግንባታው ደግሞ 22 በመቶ ተጠናቋል፡፡ሁለተኛው የግንባታ ምዕራፍ ደግሞ እ.ኤ.አ 2015 በ|ላ ይከናወናል ፡፡

የመንገዱን ፕሮጀክት የቻይናው የባቡር  መንገድ ስራ ድርጅት  ሲ አይ ሲ ኢ ኩባንያ ያከናወነዋል፡፡ የመንገዱ ፕሮጀክት  በቻይና ባንኮች ፈንድ  የሚካሄድ ሲሆን ይህም የሁለቱ ሃገራት በንግድና ኢንቨስትመንት  ያላቸውን የጠበቀ ግንኙነት ማሳያ ነው እንደ ሲሲቴቪ ዘገባ፡፡
ምንጭ፡ ኢሬቴድ

Related topics: 
በ5 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር የባቡር መስመር ግንባታ ተጀመረ 

No comments:

Post a Comment