Friday, August 24, 2012

በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኤርትራውያን የኅዘን መግለጫ አስተላለፉ

(አዲስ አበባ ነሐሴ 18/2004)--በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ የኤርትራ ለዲሞክራሲና ሰብዓዊ መብቶች ንቅናቄ እንዲሁም በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኤርትራዊያን ተወላጆች በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ዜና ዕረፍት የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ገለጹ።

በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ የኤርትራ ለዲሞክራሲና ሰብአዊ መብቶች ንቅናቄ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በላከው መግለጫ ንቅናቄው፣ ኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ ቀንድና መላው አፍሪካ በሳል መሪ አጥቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ከድህነት ለማውጣት የቻሉ የልማት አርበኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የኤርትራውያን ማህበር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ዕረፍት መላው ሰላም ወዳድና ነፃናት ናፋቂ ኤርትራውያን ሁሉ መጎዳታቸውን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ ቀደም የጀመረውን የኤርትራ ለዲሞክራሲና ሰብዓዊ መብቶች ንቅናቄና የኤርትራውያን ተወላጆች ማህበር ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ቤተሰቦች፣ የሥራ ባልደረቦችና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጽናናትን ተመኝተዋል ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው።
Source: ENA

No comments:

Post a Comment