Thursday, September 22, 2011

የመን የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን የኢትዮጵያ ኤምባሲ

(21.09.2011, የጀርመን ሬድዮ)--አንዳድ ኢትዮጵዉያን በሠነዓ-የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያዉያኑን ለመርዳት ብዙ አልሞከረም የሚል ወቀሳ ይሰነዝራሉ።

በኤምባሲዉ የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ አስተባባሪ አቶ አምደሚካኤል አድማሱ ግን ወቀሳዉን አይቀበሉትም
የየመኑ ፕሬዝዳት የዓሊ አብደላ ሳሌሕን አገዛዝን የሚቃወሙ የሐገሪቱ ዜጎች የጀመሩት አመፅ እየተጠናከረ ሲሔድ፥ እዚያ የመን የሚኖሩና የተጠለሉ ኢትዮጵያዉን ለችግር፥ አንዳዴም ለጥቃት መጋለጣቸዉን እያስታወቁ ነዉ።

ሰሞኑን ደግሞ በየመን አቋርጠዉ ወደ ስዑዲ አረቢያ ለመሻገር የሞከሩ በሺሕ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን ሁለቱን ሐገራት በሚያዋስነዉ ሐራድሕ በተባለዉ የየመን ግዛት መቃረጣቸዉ ተዘግቧል።

አንዳድ ኢትዮጵዉያን በሠነዓ-የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያዉያኑን ለመርዳት ብዙ አልሞከረም የሚል ወቀሳ ይሰነዝራሉ።በኤምባሲዉ የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ አስተባባሪ አቶ አምደሚካኤል አድማሱ ግን ወቀሳዉን አይቀበሉትም።ተክሌ የኋላ አቶ አምደሚካኤልን በስልክ አነጋግሯቸዋል።
የጀርመን ሬድዮ

No comments:

Post a Comment